ቀን፡ ነሐሴ 8/2004 ዓ.ም.
ቁጥር፡ ሐካሬ-ጠአ-555-/04
ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ!!! [አስቸኳይ]
ሐበሻ ካፌና ረስቶራንት ደንበኞቹን ለማርካት በሚያደርገው ጥረት ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት የሥራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። አመልካቾቹ እስከ መስከረም 10/2005 ዓ.ም. ድረስ በአካል ፋቢዮ ፌራረ በሚገኘው የድርጅቱ መስሪያ ቤት የሰው ኃይል አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 11 ወይም በፋክስ ቁጥር ዝም-ጭጭ ማመልከት ይችላሉ። ለሁሉም የስራ መደቦች የጽሑፍ፣ የቃልና የተግባር ፈተና የሚሰጥ ሲሆን ቀኑን በውስጥ ማስታወቂያ የምንገልጽ መሆኑን ከወዲሁ ለማስታወቅ እንወዳለን።
1. የስራ መደቡ መጠሪያ፡ ቋሚ ተሰላፊ
የሚያስፈልገው የት/ት ዝግጅት፡ በመብል ከታወቀ ከፍተኛ ተቋም በማስተርስ ወይም ከዚያ በላይ የተመረቀ፤ በሙያው ቢያንስ 18 ዓመት ልምድ ያለው፣ ጾታ፡ ወንድ ወይም ሴት፤ እድሜ 18 እና ከዚያ በላይ፤ ቢያንስ በቀን አንዴ መብላት የሚወድ፤ ድምዎዝ፡ በድርጅቱ እስኬ መሰረት ሆኖ ትርፍራፊም እንደየሆኔታው ሊኖረው ይችላል፤
2. የስራ መደቡ መጠሪያ፡ አስተናጋጅ የሚያስፈልገው የት/ት ዝግጅት፡ በኢትዮጵያዊ መስተንግዶ ከታወቀ ከፍተኛ ተቋም በማስተርስ ወይም ከዚያ በላይ የተመረቀ፤ በሙያው ቢያንስ 10 ዓመት ልምድ ያለው፣ ጾታ፡ ወንድ ወይም ሴት፤ እድሜ 18 እና ከዚያ በላይ፤ ድምዎዝ፡ በድርጅቱ እስኬ መሰረት ሆኖ እንደ ቋሚ ተሰላፊው ብዛት ጥቅማጥቅም እንደየሆኔታው ሊኖረው ይችላል፤
3. የስራ መደቡ መጠሪያ፡ ምግብ ሰሪ የሚያስፈልገው የት/ት ዝግጅት፡ በሆቴል አስተዳደር ወይም በምግብ ዝግጅት ከታወቀ ከፍተኛ ተቋም በማስተርስ ወይም ከዚያ በላይ የተመረቀ፤ በሙያው ቢያንስ 5 ዓመት ልምድ ያለው፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሱ ምግብ ሰርቶ ማሳየት የሚችል፤ ጾታ፡ ወንድ ወይም ሴት፤ እድሜ 18 እና ከዚያ በላይ፤ ድምዎዝ፡ በድርጅቱ እስኬ መሰረት ሆኖ እንደ ቋሚ ተሰላፊው ብዛት ጥቅማጥቅም እንደየሆኔታው ሊኖረው ይችላል፤
4. የስራ መደቡ መጠሪያ፡ ዘበኛ የሚያስፈልገው የት/ት ዝግጅት፡ በአድዋ ጦርነት ጊዜ አያቱ ወይም አባቱ የተዋጉ እና ታሪኩን በድንብ የሰማ፤ በሙያው ቢያንስ 10 ዓመት ልምድ ያለው፣ ጾታ፡ ወንድ ወይም ሴት፤ እድሜ 18 እና ከዚያ በላይ፤ ድምዎዝ፡ በድርጅቱ እስኬ መሰረት ሆኖ እንደ ቋሚ ተሰላፊው ብዛት ጥቅማጥቅም እንደየሆኔታው ሊኖረው ይችላል፤
ለሁሉም የሥራ መደቦች የሥራ ሰዓት እንደ አስፈላጊነቱ የሚቀያየር ቢሆንም ቋሚው ግን ከ12፡30 እስከ 14፡30 በመ.አ.ሰ. አቆጣጠር ይሆናል።
ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።
ሐበሻ ካፌና ሬስቶራንት!
--
______________________________________________________________
Alemnew Sheferaw Asrese,
University of Trento (
Masters of Science Computer Science)
Via Brennero 150, Room 005
38121
Trento (TN), ITALY
_____________________________________________________________________________________
|Nota Bene: I wonder if you send an ACK for correctly received emails.
___________________________________________________________________________